Quantcast
Channel: ተሟገት
Viewing all articles
Browse latest Browse all 1275

በባህር ዳር ታስረው የነበሩ 36 ነጋዴዎች በዋስ ተፈቱ

$
0
0

 

ባለፈው ዓመት በባህር ዳር ከተማ የሞቱ ዜጎችን ለማሰብ ነሐሴ 1 ቀን 2009 ዓ.ም. በተጠራው የሥራ ማቆም አድማ ተሳትፈዋል ተብለው ታስረው የነበሩ 36 ነጋዴዎች መፈታታቸውን፣ የከተማዋ ፖሊስ መምርያ አስታወቀ፡፡

የመምርያው ኃላፊ ኮማንደር ዋለልኝ ዳኘው ሐሙስ ነሐሴ 25 ቀን 2009 ዓ.ም. ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ ነሐሴ 1 ቀን 2009 ዓ.ም. በከተማዋ ውስጥ ያሉ ነጋዴዎች መደብሮቻቸውን እንዲዘጉና የትራንስፖርት አገልግሎታቸውን እንዲያቋርጡ ግፊት ሲያደርጉ ነበር፡፡ በዚህም ሳቢያ በርካታ ነጋዴዎች በከተማዋ ፖሊስ መምርያ በቁጥጥር ሥር ውለው የነበረ ቢሆንም፣ 36 ነጋዴዎች የዋስ መብታቸው ተከብሮላቸው ተፈትተዋል፡፡ እንደ ኮማንደሩ ገለጻ ፈጽሙታል የተባለው ወንጀል ዋስትና የሚከለክል ሆኖ ባለመገኘቱ ከእስር ተለቀዋል፡፡

እነዚህ 36 ግለሰቦች በከተማዋ ውስጥ ከፍተኛ ሀብት ያላቸው እንደሆኑ ጠቅሰው፣ ከእነዚህ መካከልም የድብ አንበሳ ሆቴል ባለቤት አቶ ሽባባው የኔአባት እንደሚገኙበት ጠቁመዋል፡፡

ኮማንደር ዋለልኝ እንደሚሉት በከተማዋ ነሐሴ 1 ቀን 2009 ዓ.ም. ተደርጎ በነበረው የሥራ ማቆም አድማ ሌሎች ተጠርጣሪዎችም ተይዘዋል፡፡ ከእነዚህ መካከልም ቦምብ በማፈንዳት የተጠረጠሩና ለዚህ ድርጊት ግብረ አበር በመሆን የተሳተፉ እንደሚገኙበት ጠቁመዋል፡፡ እነዚህ ተጠርጣሪዎች በአሁኑ ወቅት ከ20 በላይ እንደሆኑ ገልጸው፣ ጉዳያቸውም በፍርድ ሒደት ላይ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት በባህር ዳር ከተማ ያለው ሁኔታ ሰላማዊና የተረጋጋ መሆኑን  የጠቆሙት ኃላፊው፣ የተፈጠረው መረጋጋት እንዳይደፈርስ የፖሊስ መምርያው ከሌሎች አካላት ጋር በመሆን እየሠራ ነው ብለዋል፡፡

 

Standard (Image)

Viewing all articles
Browse latest Browse all 1275

Trending Articles